አገልግሎቶችን በራስዎ ቋንቋ ያግኙ

የቋንቋ ተደራሽነት መብትዎ

የስቴት ፕሮግራሞችን፣ ጥቅማ ጥቅሞችን እና አገልግሎቶችን በራስዎ ቋንቋ የማግኘት መብት አሎት። ከልጆች፣ ወጣቶች እና ቤተሰቦች መምሪያ (Department of Children, Youth, and Families, DCYF) ጋር ሲገናኙ፣ የመንግስት ጥቅማ ጥቅሞችን ወይም አገልግሎቶችን ሲጠይቁ፣ ወይም ስልጠና ወይም ዝግጅት ላይ ሲገኙ የትርጉም አገልግሎቶችን ማግኘት እና አስፈላጊ ሰነዶችን በሚፈልጉት ቋንቋ ማስተርጎም ይችላሉ።

የቋንቋ አገልግሎቶችን ያግኙ

የቋንቋ አገልግሎቶችን ለማግኘት እባኮትን ከDCYF ተወካይ ጋር በቀጥታ ይስሩ ወይም ለ Language Access (ቋንቋ መዳረሻ)dcyf.languageaccess@dcyf.wa.gov ኢሜል ይላኩ። 

ሌሎች ጠቃሚ ግብዓቶች

የልጅ ጥቃትን ወይም ቸልተኝነትን ሪፖርት ያድርጉ

1-866-363-4276

አላግባብ መጠቀምን፣ ቸልተኝነትን፣ ፈቃድ ያልተሰጠው የልጅ እንክብካቤ እና የልጅ እንክብካቤ ስጋቶችን ሪፖርት ለማድረግ። ኦፕሬተር የእርስዎን ቋንቋ ከሚናገር አስተርጓሚ ጋር ሊያገናኝዎት ይችላል።

የህዝብ ግንኙነት

ConstRelations@dcyf.wa.gov | 1-800-723-4831 | 360-902-8060

የህዝብ ግንኙነት የህፃናት ጥበቃ እና ደህንነት ጉዳዮች፣ የጉዲፈቻ እና የህፃናት እንክብካቤ ፈቃድ አሰጣጥ፣ የህፃናት እንክብካቤ ፕሮግራሞች እና የወጣቶች ማገገሚያ አገልግሎቶች ጋር በተያያዙ ቅሬታዎች ላይ ፍትሃዊ እና ጨዋነት የተሞላበት መፍትሄ የሚሰጥ ሂደትን ያቀርባል።

DCYF ማዕከላዊ የቅበላ መስመር

1-866-363-4276

DCYF ለቤተሰቦች ብዙ ግብዓቶች አሉት። ከነዚህም ጥቂቶቹን ወደ ነጻ የቅበላ መስመር በመደወል ማግኘት ይችላሉ። ኦፕሬተር የእርስዎን ቋንቋ ከሚናገር አስተርጓሚ ጋር ሊያገናኝዎት ይችላል። 

አገልግሎቶች የሚከተሉትን ያካትታሉ፦ 

  1. ከ0 እስከ 3 አመት ለሆኑ ህፃናት የሚሰጡ የቀደምት አገልግሎቶች።
  2. በስቴት ደረጃ ድጋፍ፣ ትምህርት እና የአመራር ፕሮግራሞች።
  3. ደህንነቱ የተጠበቀ እና ተመጣጣኝ የልጆች እንክብካቤ ለማግኘት እገዛ።
  4. የቤት ጉብኝት፣ የማህበረሰብ አገልግሎት እና የገንዘብ ድጋፍ።
  5. ለአካባቢያዊ የማህበራዊ አገልግሎቶች እና እርዳታዎች ሪፈራሎች።

የመድልዎ ቅሬታ ያቅርቡ

የአሜሪካውያን የአካል ጉዳተኞች ህግ (Americans with Disabilities Act)፣ የማገገሚያ ህግ ክፍል 504 (Rehabilitation Act)፣ የሲቪል መብቶች ህግ (Civil Rights Act) ርዕስ ስድስት (Title VI)፣ የቋንቋ ተደራሽነት እና የተጠበቁ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ የሚደረግ መድልዎ ቅሬታዎችን ለማቅረብ፣ እባክዎን የ DCYF የአገልግሎት ተደራሽነት እና የሲቪል መብቶች ቅሬታ ቅጽን

ይሙሉ።